ህጻናት ክትባት ከወሰዱ በኋላ ቤተሰብ ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮች

ከክትባት በኋላ ክትባቱ እየሰራ እንደሆነ የሚጠቁሙን መለስተኛ ምልክቶች አሉ፡፡

እነዚህ ምልክቶች የህጻናት ሰውነት አዲስ ፀረ እንግዳ አካላትን መኖሩን የሚጠቁሙ እና በአማካኝ እስከ ሶስት ቀን ሊቆዩ የሚችሉ ምልክቶች ናቸው፡፡

☑️ ሊኖሩ የሚችሉ ምልክቶች

? የተወጉበት ቦታ ላይ መቅላት እና የህመም ስሜት
? የተወጉበት ቦታ ላይ አነስተኛ እብጠት
? ማልቀስ እና መነጫነጭ
? መጠነኛ ትኩሳት
? ማስመለስ
? የምግብ ፍላጎት መቀነስ

 ☑️ ምልክቶች እንዳይባባሱ መደረግ ያለባቸዉ ነገሮች

? በማባበል እና በማጫወት ሃሳባቸውን ለመስረቅ መሞከር
? የተወጉበትን ቦታ አለመንካት
? ቶሎ ቶሎ ጡት ማጥባት ወይም ትንሽ ትንሽ ቶሎ ቶሎ መመገብ
? ትኩሳቱን በመለካት ከ37.5 °C በላይ ከሆነ ንጹህ ፎጣ ቀዝቃዛ ዉሃ ዉስጥ በመንከር ለማቀዝቀዝ መሞከር የማይበርድ ከሆነ የትኩሳት ማብረጃ መድሐኒቶችን መስጠት

☑️ መቼ  ባለሙያ ማማከር አለብኝ?

↪️ የትኩሳት ማብረጃ መድሐኒት ተወስዶ ትኩሳት የማይቀንስ ከሆነ
↪️ ሙሉ ለሙሉ የመጥባት ወይም የመመገብ አለመቻል
↪️ በተደጋጋሚ ማስመለስ ካለ
↪️ የቆዳ ከለር መቀየር ካለ/ነጭ የመሆን/
↪️ አቅም ማጣት/የተባባሰ የድካም ስሜትየሰዉነት ማንቀጥቀጥ
↪️ ትንፋሽ ማጠር/ቶሎ ቶሎ መተንፈስ
↪️ የልብ ምት መጨመር

ዶክተር መሐመድ በሽር የህፃናት እስፔሻሊስት